Friday, August 23, 2013

የመጀመሪያይቱ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት በቆሮንቶስ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መግቢያ



የመጀመሪያይቱ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት
በቆሮንቶስ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን
መግቢያ
v  የቆሮንቶስ ከተማ
መልክዓ ምድር:
·         ከግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ 75 ኪ.ሜ ትርቃለች
·         በሁለቱ የግሪክ ጠቅላይ ግዛቶች /አኪያና መቅዶኒያ/ መካከል ባለው ልሳነ ምድር ላይ የተገነባች ከተማ ነበረች
·         የአካያ ጠቅላይ ግዛት ዋና ከተማም ነበረች
·         የሮማው ምክትል ቆንሲል መቀመጫም ስለነበረች ብዙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ነበሩባት
1.   ንግድ
·         በብዙ የባሕር ወደቦች የተከበበች ከተማ በመሆኗ ከልዩ ልዩ  የዓለም ክፍል የተሰበሰቡ ነጋዴዎች በከተማዋ ይኖሩ ነበር። በዚህም ታላቅ የንግድ ማዕከል ሆነች
·         ከሮም ወደ ምስራቅ ለሚደረገው ታላቅ የንግድ ጉዞ ሁነኛ የባሕርይ መሸጋገሪያ ነበረች
·         ከብልጥግናዋ እና ከስልጣኔዋ የተነሣ እጅግ የከፋ ኃጢአት የሚደረግባት ከተማ ሆነች። ከዚህ የተነሣ ቆሮንቶሳዊ መሆን የእፍረት ምክንያት እስከመሆን ደርሶ ነበር።
·         ቆሮንቶስ በራዕይ ዮሐንስ ላይ የተጠቀሰችውን ባቢሎን እስክመምስል ደርሳ ነበር  ራዕ 18፥2፤ ራዕ 17፥5
2.   ሃይማኖት
·         የተለያዩ  ሃይማኖቶች የአይሁድ እምነትን ጨምሮ  በከተማዋ ነበሩ
·         ከ20 በላይ የጣዖት መቅደሶችም ነበሩባት
·         የአይሁድ ምኩራብም እንዲሁ በዚያው ነበር   ሐዋ 18፥1
·         አፍሮዲቴና leእርሷ የተቀደሱ 1000 ሴተኛ አዳሪዎች ነበሩ   ሮሜ 1፥26
3.   ማኅበራዊ እንቅስቃሴ
·         ከንግድ ከተማነቷ ጋር ተያይዞ ስፖርት፣ ቲያትር  እና ሥነጥበብ በቆሮንቶስ ይዘወተሩ ነበር
·         ሮማውያን፣ አይሁዶችና ግሪኮች የሚኖሩባት ከተማ በመሆኗ ማኅበራዊ እንቅስቃሴውና ባሕሉ ቅይጥ ነበር
·         አብዛኛዎቹ ነዋሪዎችና ነጋዴዎች ግሪኮች ስለነበሩ የከተማዋ የሥራ ቋንቋ ግሪክኛ ነበር
·         ሐዲስ ኪዳን ወደ አሕዛብ ምድር ከገባበት ዘመን 600 ሺህ ሕዝብ የሚኖርባት ታላቅ ከተማ ነበረች።
v  የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን
·         በሐዋርያው ጳውሎስ ሁለተኛ የወንጌል ጉዞ  ተመሰረተች።  ሐዋ 15፥36፤ 16፥6
·         ጊዜው ከ50-52 ዓ.ም ሲሆን በዚህ ወቅት ጳውሎስ በቆሮንቶስ ከአንድ ዓመት ከስምንት ወር በላይ ተቀምጧል። 
·         በምኩራብም ተሳዳቢዎች ስለበዙ ያመኑትን ነፍሳት ለይቶ በአንድ ግለሰብ ቤት በማስተማር አገልግሎቱን ጀምሯል   ሐዋ 18፥6
v  የቆሮንቶስ ክርስትና
·         ለፍጹማን እንኳን ፈታኝ የሆነ ትግል ውስጥ ነበረች
·         የቆሮንቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብታ ነበር
·         አብዛኞቹ ድሆችና ጥቂት ባለጠጎች የነበሯት ቤተክርስቲያን በመሆኗ ቆሮንቶሳዊneት /መለያየት/   ገላ 5፥21 ለተባለው ኃጢአት ተላልፈው እንዲሰጡ ይህንን ሰይጣን እንደ ልዩነት ምክንያት ያሳያቸው ነበር፡- የአጵሎስ፣ የጳውሎስ፣ የኬፋ፣ የክርስቶስ በመባባል
·         በአሕዛብ መካከል በቁጥር ትንሽ ስለነበሩ እጅግ ይጨነቁ ነበር   2ቆሮ 2፥7
·         ጋብቻ መፈጸምና፣ ለጣዖት ያልተሰዋ ሥጋ ማግኘት እንኳን ከባድ ነበር::
v  መልዕክቱ የተጻፈበት ምክንያት:
1.   በቤተክርስቲያኒቱ ኃጢአትና ርኩሰት ዝሙት 1ቆሮ 5፥1 ፤ መለያየት  1ቆሮ 1፥11 ፤ መፈራረድ 1ቆሮ 6፥1 ፤ ለጌታ ክብር አለመሰጠት 1ቆሮ 11፥1 ስለበዛ ተግሳጽና ምክር ለመስጠት
2.   ሃይማኖታዊ ክርክሮችና ጥያቄዎች ስለበዙ መልስ ለመስጠት
·         ስለ ትንሳኤ ሙታን    1ቆሮ 15፥1 እስከ ፍጻሜው
·         ስለጌታ ራት    1ቆሮ 11፥1-16
·         ስለ ጋብቻ     1ቆሮ  7፥1 እስከ ፍጻሜው
·         በመንፈስ በጽድቅ ስለማደግ   1ቆሮ 3፥1-5
v  የመልዕክቱ ዋና ሐሳብ
·         በቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተነሳውን ማዕበል ማቆም
·         ቅርጽ ያለው የቤተክርስቲያን አደረጃጀት መፍጠር
·         ቤተክርስቲያኒቱን ወደ ውበቷ መመለስ
·         አማኞችን ከአባልነት ወደ አካልነት ማሳደግ
·         ከእጮኝነትም አልፈው ለሚስትነት እንዲዘጋጁ ማድረግ
v  የመልዕክቱ ጸሐፊ  -    ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
-          መንፈስ ቅዱስ
·         የጻፈው በኤፌሶን ተቀምጦ ሳለ  ከ55-56 ዓ. ም ባለው ነው።

1 comment:

  1. የመምህር በሪሁን ገጽ: የመጀመሪያይቱ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት በቆሮንቶስ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መግቢያ >>>>> Download Now

    >>>>> Download Full

    የመምህር በሪሁን ገጽ: የመጀመሪያይቱ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት በቆሮንቶስ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መግቢያ >>>>> Download LINK

    >>>>> Download Now

    የመምህር በሪሁን ገጽ: የመጀመሪያይቱ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት በቆሮንቶስ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን መግቢያ >>>>> Download Full

    >>>>> Download LINK

    ReplyDelete