Monday, July 29, 2013

የሞት መድሀኒት

      እርሱ:-  ዘመናት ሳይፈጠሩ አስቀድሞ ለዘላለም ሃሳቡ አዘጋጀን፡፡ 
በሀጢያታችንም ሙታን ሳለን ወደደን፡፡ስለወደደንም መላዕክትን እንካን ሳይመስል እኛን መሰለ፡፡የጸጋ ሁሉ አምላክ ከአህያና ከላም ሙቀት ለመነ፡፡ በዚህም መዋረዳችንን ወስዶ ክብር አለበሰን፡፡አሁን ከእርሱ የተነሳ እንደ ባለ መዕለግ እንደ ባላማል ተቆጥረናል፡፡አሁን የምንተማመንበተ መርከብ ፤የምንደርስበት ወደብ አለን፡፡አባት አለን፡፡ልጆች ነን፡፡ወራሾች ነን፡፡ በሀጢያታችን የሚራራ ሊቀ ካህን አለን፤ከእስትንፋሳችን በላይ ቅርብ ነዉ ከመድህንና ከኢንሹራንስ ቀድሞ ይደርስልናል፡፡
ከምንምገዉ አየር በላይ ያስፈልገናል፡፡
በመስቀሉ ጥልን አስወግዶ በሞቱ ጠላት ገሎ
   በፋሲካዉ ሌሊት በዚያ ግሩም ሌሊት አጽድቆናል፡፡እናታችንም አባታችም እህታችንም ወንድማችንም ነዉ፡፡በምንም የማንመዘነዉ በማንም የማንቀይረዉ ዉዱ ገንዘባችነ ነዉ፡፡እናምነዋለን ከሕጻንነታችነን ዘመን ጀምሮ ጠብቆናለ ይህን ሁሉ ዘመን መግቦናል በብዙ በረከት አሳድጎናል ለኛ ያለዉ ገና ብዙ ነዉ፡፡
ይሄን ጌታ በምስጋና ላይ ምስጋና በቅኔ ላይ ቅኔ እየጨመርን እንዳበደ ሠዉ ዘመናችንን    ሙሉ ርቃናችንን ሆነን ብናገለግለዉ ያንስበታል እንጅ አይበዛበትም፡፡ይገባዋል፡፡          እርሱ ባለ    ዉለታችንነዉ፡፡                                                                              ስሙ ኢየሱስ ነዉ፡፡መድሐኒት::ያዉም የሞት መድሀኒት::

1 comment:

  1. "መድሐኒት::ያዉም የሞት መድሀኒት::",,kale hiwet yasemaln!!!

    ReplyDelete