Tuesday, July 23, 2013

ያልተቆረጠ ማንነት

    
                                                  ማር 1313-31

      ጌታ በምሳሌ ካስተማረባቸዉቀናት በአንዱ ከህጻንነቱ ጀምሮ የሙሴን ህግጋት የጠበቀ በነቢያት የተነገረዉን ሁሉ የሚፈጰም ሰዉ ወደ እርሱ ቀረበና የዘለዓለም ሕይወት እንድወረስ ምን ላድርግ ሲል ጠየቀዉ ASየዘለዓለም ሕይወት ማለት የማይቁረጥ ሕያዉነት ማለት ነዉ፡፡ ይህ ሕያዉነት ሶስት መልክ አለዉ፡-

1.      የእግዚአብሔር ሕያዉነት፡-ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም የሆነ ሕየዉነት ነዉ፡፡ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የቁጥር መጀመረያ በሌለዉ ዘለዓለማዊነት አምላክነቱ አምላክነቱን እየባረከዉ በብርሃናዊነቱ ብርሃን በብርሃን ተከቦ ክብሩ ከብሩን እያወደሰዉ ቅድስናዉ እየቀደሰዉ ብቻዉን ይኖር ነበር፡፡ በዘመናትም መካከል ሕያዉ ነዉ፡፡ ከዚህም በኋላ ማለቂያ በሌለዉ የጊዜ ዑደት ከዘመናት ቁጥጥር ዉጭ በመሆን ዓመታትን እንደ ጨርቅ እያስረጃቸዉ ሕያዉ ሆኖ ይኖራል፡፡

2.     የመላእክት እና የሰዉ ሕያዉነት፡- አስቀድመዉ አልነበሩምና ከተፈጠሩበት ዕለት ጀምሮ እስከ ዘለዓለም ሕያዋነ ነቸዉ፡፡
3.     የግዑዛንና የእንስሳት ሕያዉነት፡- አስቀድመዉ አልነበሩም ወደፊትም አይኖሩም ከተፈጠሩበት ጊዜ እስከ ሚጠፉበት (ሚሞቱበት) ጊዜ ሕያዋን ናቸዉ፡፡

የህግ ጠንቃቂ የዘለዓለምዊነት ጉዳይ ያሳሰበዉ ይመስላል ምክንየቱም ከሙታን ትንሳዔ በኋላም የሰዉ ሕያዉነት ይቀጥላል፡፡ ሰወችም ሕያዋን ሕያዋን ወይም ሕያዋን ሙታን ይሆናሉ፡፡ ማለትም በገሀነመ እሳት ወይም በመንግስተ ሰማያት የሚኖረዉ ይለያል፡፡ በተለይ ጌታ መንግስቱን በሕጻናት ምሳሌ ከሰበከ በኋላ በእግዚአብሔር መንግስት ዉስጥ ሕያዉ ሆኖ መኖር ሰወች የተፈጠሩበት ዋና ዓላማ እንደሆነ ገብቶታል፡፡ ነገር ግን ያንን የሕይወት መንገድ አላወቀዉም ከልጅነት ወራቱ ጀምሮ የጠበቃቸቸዉ ህግጋትም እርግጠኛ አላደረጉትም፡፡ለዚህም ነዉ ጌታ ከሙሴ ህግ ጠቅሶ፡-አትስረቅ ፤ አትግደል ፤ አታመንዝርሲለዉ እነዚህንማ ከልጅነቴ ጀምሮ ጠብቄያለሁ በማለት ከህግ በላይ የሆነ ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚወስድ አንድ መእገድ እያፈላለገ ያለዉ፡፡ አላስተዋለም እንጂ የዘለዓለም ሕይወት ከእርሱ ጋር እየተነጋገረ ያለዉ ነዉ፡፡
የቀደሙት የሰወች ሁሉ የሙሴን ህግና የቃልኪዳኑን ታቦት ትዕዛዝ ያለነቀፋ ጠብቀዉ ነበር ነገር ግን ህግ ፈረደባቸዉ እንጅ ለደህንነታቸዉ አልሆነም ፡፡ማንም ሰዉ ያለ እግዚአብሔር ምህርት ትምክህት የለዉም ከታላቁ አምላካችንና አባታችንና ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳ እንጅ ህግጋትን በመፈጰም ማንም ወደዘለዓለም እረፍት አልደርስም፡፡ ጰጋዉ ካልረዳ በቀር ህግ በድካም እየፈረደ አንድስ እንካን የሚተርፍ አይኖርም፡፡እያንዳንዳችን ለህግ ቀጣት የሚሆን ማንነትና ድካም በዉስጣችእ አለ፡፡

       የሰዉየዉን ሁኔታ ስናጠናዉ ፍጹም ለመሆን የፈለገ ይመስላል፡፡ ጌታም ሀሳቡነ ወደደለትና ያለህን ለድሆች ሰጥተህ ተከተለኝ አለዉ (በሙሴ ህግ ራስህነን ትጠብቅ ነበር አሁን ለልሎች ትረፍ አለዉ) ሰዉየዉ ወደ ክርስትና ሊመጣ ነዉ ክርስትና ደግሞ ለልሎች መትረፍ ነዉ፡፡ ሰዉየዉ ግን አዝኖ ተመለሰ፡፡
ሰዉየዉ የሕይወት መረህ አልገባዉም ፤ ፍላጎት እንጅ ቁረጠኝነት የለዉም ፤ ስሜታዊም ነበር አሊያም እንደ ሕጰናት መሆን ማለት ጨዋታ መስሎታል፡፡በሕይወት እንቅስቃሴ ዉስጥ ሁሉም ነገር ዋጋ አለዉ ለማግኝት ማጣት ከፍ ለማለት ዝቅ ማለት ያስፈልጋል ሳይከፈል የሚወሰድ ነገር የለም፡፡ አስፈላጊ ለሆነ ነገር ዋጋ አለመክፈልም ራሱ የሚያስከፍለዉ ዋጋ አለ (not taking of a risk also risk )እንደሚሉት፡፡ የዘለዓለም ሕይወት ይፈልጋል ገንዘቡን ማጣት አይፈልግም ፤ እግዚአብሔርን ማምለክ ይፈልጋል ከሌላዉ አምላክ (ገንዘብ) ጋር አንደ ተጋባ ነዉ፡፡ልናሰታዉሰዉ የሚገባዉ ነገር ማንም መብቱን ለመጠቀም ሲያስብ ግጌታወቹን መወጣት የግድ መሆኑን ነዉ፡፡

         በሁለት ሀሳብ ማንከስ ለሁለት ጌታ መገዛት ጠፍንጎ የያዘን የጋራ ችግራችን ነዉ፡፡ (ተረት) አንድ ሰዉ ገደል ሊገባ ሲል አፋፉ ላይ ዛፍ አገኘና ተንጠለጠለ አመሰግኖ ሳያበቃ ዛፍዋ መወዛወዝ ጀመረች ጌታ ሆይ አድነኝ እያለ መጮሁን ተያያዘዉ ጌታም መጣና አድንሀለሁ የምታምነኝ ከሆነ ዛፍን ለቀቅዉ አለዉ ሰዉየዉ መላሶ አይ እግዚአብሔር አንተንም አምናለሁ ዛፍንም እይዛለሁ አለ፡፡ የመወሰን ችግር ፤ እርምጃ የመዉሰድ ችግር ፤ ነገን መፍራት ፤ ያለንበትነ ሁኔታ እነደ መቹ ማረፊያ መቁጠር ፤ ከመለኮታዊ ጥበቃ ይልቅ በዙሪያች ባሉ ሁኔታወች መደገፍ፤ባሮጌዉ እርሶ መቡካት ፤ በዱሮዉ ልምምድ መኖር ፤ ቀላቅሎ ለመኖር ምሞከር (መዝሙርም ጋር ዘፈንም ጋር ፤ ጣዖትም ጋር ታቦትም ጋር….) መዉጊያወቻችነን ናቸዉ ፡፡ መሀል ሰፋሪ በሁለት ጥይት ይመታልና አንዱን መቁረጥ ይገባል የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ፡፡ እነደዚህ አይነት የመንፈስ ዝለት እግዚአብሔርን በእግዚአብሔርነቱ መጠን ካለማምን የሚመነጭ ነዉ፡፡ይህ ደግሞ የክረስቶስ መልከ እንዳይኖረን ዉበታችንን እያጠፋ የጎሳቆለን አረም ነዉ፡፡ልንቆርጠዉ ይገባል እግዚአብሔር ያግዘን፡፡

       ወዳጆቸ፡- የማንወደውን እያደረግን የምንወደዉን ማድረግ ከተሳነን ሰነበትን፡፡ እስኪ በእግዚአብሔር ፊት እንሁን ለችግሮቻችን ሁሉመፍትሄ ያለዉ እርሱ ጋር ነዉ፡፡ይቆየን፡፡በመንፈስ ቅዱስ ሰለትነት ያረጀዉን ማንነት ይቁረጥልን አዲስ መንፈስና አዲስ ልብ ያድለን፡፡አሜን፡፡

ምስጋናና ዉዳሴ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ሕያዉ ለሆነዉ ይሁን፡፡አ ን፡፡፡፡፡

No comments:

Post a Comment